የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት በዋና ዳይሬክተርና በምክትል ዋና ዳይሬክተር መሪነት በስምንት የምርምር የስራ ሂደቶች፣ በዘጠኝ የአስተዳደር ዘርፍ የስራ ሂደቶች፣ በሰባት የብዝሀ ሕይወት ማዕከላት፣ በሁለት እፅዋት አጸድ ማዕከላት እና በአንድ ዘረ-መል ባንክ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ብዝሀ ሕይወት ኢንስቲትዩት ስምንት የምርምር የስራ ሂደቶች ያሉት ሲሆን እነሱም፡-

    • አዝርዕትና ሆርቲካልቸር ብዝሀ ሕይወት ዳይሬክቶሬት
    • እንስሳት ብዝሀ ሕይወት ዳይሬክቶሬት
    • ደቂቅ አካላት ብዝሀ ሕይወት ዳይሬክቶሬት
    • ደንና ግጦሽ መሬት እፅዋት ብዝሀ ሕይወት ዳይሬክቶሬት
    • የጀነቲክ ሀብት አርክቦትና ጥቅም ተጋሪነት ዳይሬክቶሬት
    • የስርዓተ ምህዳር ዳይሬክቶሬት
    • የቅርንጫፍ ማዕከላትና ባለድርሻ ሴክተሮች ዳይሬክቶሬት
    • የምርምር፣ ስርጸትና ፕሮጀክት ትግበራ ዳይሬክቶሬት

እንዲሁም ዘጠኝ የአስተዳደር ዘርፍ የስራ ሂደቶች እነሱም፡-

    • ሕዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
    • የግዢ፣ ፋይናንስ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
    • የውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት
    • የእቅድ፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት
    • የሰው ሀብት ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
    • ኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክቶሬት
    • ለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት
    • የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
    • የስነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት